Thursday, November 23, 2006

ለኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንጩህላቸው !!
choreber (ጮሬበር)Blogger

በሱዳንና በእንግሊዝ ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እየተያዙ ለአምባገነኑ የመለስ ዜናዊ አገዛዝ ሊሰጡ መሆኑን ከኢንተርኔት ላይ እያነበብን ነው ። ሁላችንም እንደምናውቀው ዛሬ ፤ ኢትዮጵያ ፤ የፖለቲካ ፕሮግራማቸውን በሰላማዊ መንገድ ብቻ ሲያራምዱ የቆዩ ኢትዮጵያውያን ፤ መሳሪያ ያልታጠቁና በብዕር ብቻ ነፃ አመለካከታቸውን በነፃ ጋዜጦች ሲገልፁና ለህዝቡም ነፃ አንደበት የሁኑለት ነፃ ጋዜጠኞች ፤ የህዝቡን ሰብዓዊ መብቶች ለማስከበር በሚያደርጉት ትግል የታወቁ ግለሰቦች ፤ የመምህራን ማህበር አመራር አባሎችና መምህራን ፤ ከአንደኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፤ ነጋዴዎችና አምባገነን ሥርዓትን የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ፤ ዘር ፤ ፃታና ህይማኖት ሳይለይ የተገደሉባት ፤ የታሰሩባትና እየተዋከቡ የሚኖሩባት ሃገር ናት ።

ኢትዮጵያ ወደ መግደያ ቻምበር እና እስር ቤት ከተለወጠች ቆየች ። መሪዎቿም የአፍሪካ የዘመኑ ናዚዎች ሆነዋል ። ከሰብዓዊ ፍጡርነት ወደ አውሬነት ራሳቸውን ከለወጡ ብዙ ጊዜያቸው ነው ። ለዚህ ሥርዓት አልባ መንግሥት ለሚመስል መንግሥት ነው ኢትዮ ጵያውያን ከየተገኙበት እየታነቁ የሚሰጡት ። ሁላችንም ራሳችን ላይ እንዲደርስ በማንፈልገው ሁኔታ ውስጥ ነው ያሉት ። እናም እንድረስላቸው !! አንብበን ዝም አንበል ። ሰምተን ዝም አንበል ። ምራቅ መምጠጥ ብቻ አይበቃም ። ብናምንም ባናምንም ለኛ ለኢትዮጵያውያን ከራሳችን ውጭ ማንም የለንም ። ማንም አይረዳንም ። ብዙ ጊዜ ብዙ ቦታ አይተናል ። የሚፈልገን እንጂ የሚረዳን የለም ። የሚፈልጉን ደግሞ ለጦርነት ብቻ ነው ። ስንሞት ደስ ይላቸዋል ። ለረሃብ ብቻ ነው የሚፈልጉን ። በረሃብ ስንቆላ ደስ ይላቸዋል ። የኛ ረሃብ ለነሱ ገንዘብ ለኛ ግን ሞት ነው ። በሞታችን ይደንሳሉ ። በሞታችን ብዙ ገንዘብ ይዝቃሉ ። የኢትዮጵያውያን ሞት ለብዙዎቹ አትራፊ ኮርፕሬሽን ነው ። ስለዚህም ለወገኖቻችን እንጩህላቸው ። ለስደተኛው ህብረተሰብ እንጩህ !! በስደት አለም እየተሰቃዩ እንዳይኖሩ እንጩህ ። የኢትዮጵያዊ ነፍስ ምኑም ላልሆነው መለስ ዜናዊ እንዳይሰጡ እንጩህ ።



Wednesday, November 22, 2006

Dr. Taye and Ato Kifle Urge Renewed Moves
Ehiomedia , November 22 , 2006
Ethiopian Demonstration In Brussels
Eri-TV
At least Nine Eritrean Journalists Arrested In New Round-Up
rsf.org , November 22 , 2006
Three Eritrean Journalists Died In Prison Camp
rsf.org report on November 14 ,2006
ETHIOPIA BORDER IMPASSE UNSUSTAINABLE, SAYS ERITREA
By AFP , Middle East Times , November 22 , 2006

Eritrea Wednesday warned that the current stalemate over its tense border with Ethiopia was "not sustainable" and refused to rule out a new war against its arch-foe Horn of Africa neighbor. At the same time, Asmara repeated denials that Somalia had become a proxy battleground for it and Addis Ababa amid reports that the two countries are backing rival factions there to settle scores from their bloody 1998-2000 conflict.

Two days after Eritrea and Ethiopia both rejected plans by a UN-appointed border panel to demarcate their contentious frontier on paper, further raising tensions, a senior Eritrean official said that all options were on the table.

"Eritrea is a sovereign country and we cannot accept the reality of our territory being occupied by a foreign power indefinitely," said Yemane Gebremeskel, director of Eritrean President Issaias Afewerki's office.

"I don't want to speculate on what can happen, but I can only tell you this situation is not sustainable, it cannot be acceptable legally and there is no reason why it should stay this way," he told reporters in an interview in Asmara.

On Monday, the two nations boycotted a meeting of the Eritrea Ethiopia Boundary Commission in The Hague designed to gather comment about a proposal to delineate the border on maps without marking it on the ground.

Eritrea accepts the panel's ruling, which awarded it the flashpoint town of Badme, but wants it be physically laid out on the ground, while Ethiopia, which rejects the boundary, said that the commission was acting outside its mandate.

The commission's proposal appeared aimed at easing growing tension between the two countries that many fear could lead to a renewal of their war and spill over into Somalia, threatening a wider regional conflict.

The stalemate has left the status of the 1,000-kilometer (620-mile) border unclear six years after a peace deal and raised tensions, heightened by UN reports that both nations are militarily active in Somalia.

Yemane refused to say whether Eritrea, which has repeatedly denounced the international community for failing to press Ethiopia to accept the commission's binding ruling, would fight to take the territory in question.

But he repeatedly stressed that "all options" were open.

"As far as what our options are, I think these are options we can exercise at any point in time," Yemane said, declining to elaborate.

Yemane also denied charges by UN experts and diplomats that Eritrea is trying to exploit the situation in Somalia by arming a powerful Islamist movement that is girding for war with a weak government supported by Ethiopia.

"All these attempts to portray Somalia as a proxy battlefield between Ethiopia and Eritrea are misguided," he said. "There is no reason why we should go to Somalia to settle scores with Ethiopia."

Copyright (c) 2006 News World Communications, Inc. All rights reserved.

Tuesday, November 21, 2006

Exiled Ethiopian journalists appeal for safe exit from Kenya
Ethiomedia,November 20,2006

NAIROBI , Kenya - Ethiopian journalists living as refugees in Kenya appealed to UNHCR and the international community on Monday that they were living under the constant fear of being attacked by Ethiopian government agents and their lives be spared by being transfered to any other third country. Following is the press release issued by the exiled journalists : ( click here to read full text)

Saturday, November 18, 2006

ለሄኖክ ነጋሽ እና መላ ቤተሰቡ

የእናታችሁን ከዚህ አለም በሞት መለየት የሰማነው በከፍተኛ ድንጋጤ ነው ። ከልብም አዝነናል። እግዚአብሄር ነፍሳቸውን ይማር ከማለት ውጭ ምንም ለማድረግ እንዳልቻልን ስንገልፅላችው ፀፀት ይሰማናል። እናንተንም ፤ ባህር አቋርጠው የመጡና በቅርብም ከእናንተው አካባቢ ያሉትን የሃዘን ተካፋይ ዘመዶቻችሁን ሁሉ እግዚአብሄር ጽናቱንና ብርታቱን ይስጣችው እንላለን።

choreber (ጮሬበር) Blogger.

Ethiopian in Europe held demonstration
EMF, November 18,2006
Ethiopians in Brussels demand Zenawi be brought to justice

Ethiomedia reporter, November 17,2006
Addis Voice
Addis Voice
Addis Voice

Friday, November 17, 2006

Kifle Mulat & Dr. Taye Woldesemayat to speak in Washington, D.C.
EMF , November 15 , 2006

Kifle Mulat and Dr.Taye Woldesemayat to speak in Washington , D.C. on the coming Sunday , November 19 , 2006. Ethiopians are invited to attend a town hall meeting to receive and discuss eye witness report on the deteriorating human rights situation in Ethiopia .

The event is sponcered and organized by the famous Addis Dimts,which is based in Washington , D.C. Artist Abebe Belew , manager of Addis Dimts told EMF , it is great opportunity to meet and discuss with Ao Kifle Mulat and Dr.Taye Woldesemayat on the current situationof our country .

Dr.Taye Woldesemayat , president of Ethiopian Teachers Association (ETA) and Kifle Mulat , veteran journalist and president of Ethiopian Free Press Journalists Association (EFJA) will discuss the current human rights situation and possible courses of action to achieve a better future.

The meeting will be at Unification Church , 16th street and columbia road , NW , Washington , D.C.

2pm-6pm.


Wednesday, November 15, 2006

-----------------------------------------------------------
ERITREAN PRESIDENT ASSAILS US FOR STOKING CONFLICTS
By Emmanuel Goujon
AFP

Eritrean President Issaias Afewerki Wednesday slammed the United States for fanning conflicts in the Horn of Africa region, particularly in Somalia, where an imminent war threatens to engulf the volatile region. From Eritrea's independence struggle to its simmering border row with archrival Ethiopia and the unrest in the war-devastated Somalia, Afewerki blamed Washington for stoking the conflicts for its interests.

Tracing its role to the end of World War II, he said that Washington had favored the existence of Ethiopia over Eritrea that put up decades of armed struggle for independence from Ethiopia, of which it was formerly a province.

"Our conflict is historically [tied] with the United States," he said in an interview. "Eritrea could have enjoyed its right to self-determination after the Second World War, but the United States ... came with a global strategy deciding the fate of Eritrea to be somehow linked with Ethiopia because Ethiopia was considered to be a major proxy in the region," said Issaias, whose nation got independence in 1993.

He also blamed the United States for their unresolved border row with Ethiopia despite insisting that the matter had been resolved by the decision of an independent border commission in 2002.

"Why was it [ruling] not implemented? Because the United States doesn't want to implement the decision. They like to live on conflict. They create conflicts and exploit conflict. That's it," he said.

In addition, the Eritrean leader, himself chided for a raft of human rights violations in his tiny Red Sea state, said that Washington was using Addis Ababa as its "tools and puppets" to navigate and destabilize the region.

"We have no problem with Ethiopia ... As far as the border is concerned, it is resolved ... now, history is repeating itself and the United States is coming and complicating the situation," he added.

The Eritrean leader charged the world's superpower with fomenting fighting in lawless Somalia, where a powerful Islamic movement and a weak government are on the edge of an all-out war.

The Somali Islamists have accused Ethiopia of sending thousands of troops to Somalia to protect the government, but Addis Ababa maintains that it sent only a few hundred military advisers.

Tension soared after the Somali peace talks collapsed November 1, heightening fears of a conflict that diplomats and analysts fear could draw in Eritrea and Ethiopia on rival sides after their own unresolved 1998-2000 border war.

Eritrea has been accused of supplying weapons and sending some 2,000 soldiers to back the Islamists, with Issaias saying: "This is a crazy statement, not only false but insane."

And instead, Issaias said that Washington had accused the Somali Islamic leaders of links to terrorism groups, including Al Qaeda in order to intervene.

"We don't want the United States to be involved under the umbrella of fighting terrorism, because it will be a complication," he added.

The Islamists have rejected the planned deployment of peacekeepers, a position that Eritrea and Djibouti support.

"We support the choice of the Somali people. We don't accept, agree or condone any external intervention under any pretext," Issaias said. "Allow Somalis to find a solution to this problem, don't intervene. They might not find a solution instantly, but give them a chance to reconcile with themselves and reconstitute Somalia," he added.

Somalia has been without a functioning central authority since the 1991 ousting of strongman Mohamed Siad Barre, and the two-year-old transitional government has been unable to assert control.

Copyright (c) 2006 News World Communications, Inc. All rights reserved.

Monday, November 13, 2006

PeoplePC

Thursday, November 09, 2006

የኢትኦጵ መጽሔት ርዕሰ አንቀፅ
"ድል እያሸተተ ያለ ህዝብ ውጤቱ እንዲቀለበስ አይፈቅድም"
( ቅፅ 6 ቁጥር 70 ግንቦት 97 ዓ.ም )


ዛሬ በእስር ላይ የሚገኙት የኢትኦጵ አሳታሚና ጋዜጠኞች ለገዳዩ የወያኔ መንግሥት ከዚህ በታች የተመለከተውን መልዕክት አስተላልፈው ነበር ። ከበረሃ አውሬነት ወደ ቤተመንግሥት አውሬነት የተለወጠው የወያኔ መንግሥት ግን አልሰማቸውም ። እንዲያውም አውሬነቱን በላይ በላይ ጨመረበት እንጂ !!

"ሐሙስ ግንቦት 18 ቀን 1997 ዓ.ም በዩኤስ አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት እጅግ ደማቅ ትዕይንተ ሕዝብ እስከዛሬ በአሜሪካ ኢትዮጵያውያን ካደረጉት ሰልፍ የላቀ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ የተገኘበት መሆኑ ተረጋግጧል ። ኢትዮጵያውያን በፍፁም የወንድማማችነት ስሜት በአንድነት ቆመው በአንድ ድምፅ ለሐገራቸው ትንሳኤ ጮኸዋል ። ልዕለ ኃያል የሆነችው ዩኤስ አሜሪካ በኢትዮጵያ የተካሄደውን ምርጫ ለማዛባት የሚደረገውን ጥረትና ሂደቱን በጉልበት ለመቀልበስ የሚደረገው ጥረት እንድትከታተልና የህዝብ ድምፅ እንዳይሰረቅ ግፊት ታደርግ ዘንድ ተማፅነዋል ። የህብረቱም ይሁን የቅንጅቱ ደጋፊዎች በአንድነት በአንድነት ቆመው ድምፃቸውን ያስተባበሩበት ይህ ትዕይንት የአሜሪካውያንንም ሆነ የሌሎች ሃገሮችን ትኩረት የሳበ መሆኑንም መረዳት ተችሏል።

በመቶዎች ፣ አንዳንዴም ከዚያ በታች ፣ ግፋ ቢልም ከአንድ ሺህም የማይልቁ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ሁኔታዎችና አጋጣሚዎች በዋሽንግቶን ጎዳናዎች ላይ ሰልፍ ሲያደርጉ የታዩ ቢሆንም ፣ ከአሥር ሺህ ሕዝብ የሚልቅ ኢትዮጵያዊ በአንድነት አደባባይ ሲወጣ ይህ የመጀመሪያ ነው ። በአሜሪካ የሚኖሩየውጭ ሐገር ዜጎች በሐገራቸው ጉዳይ ላይ ተሰባስበው በእንዲህ ያለ መጠን ትዕይንተ ሕዝብ ሲያካሂዱ የኢትዮጵያውያን የመጀመሪያው መሆኑም ተነግሮለታል ። በአሜሪካ ርዕሰ መዲና ዋሽንግተን ላይ የተስተጋባው የኢትዮጵያውያን የአንድነት ድምፅ በጀርመን በርሊን ላይም ተስተጋብቷል ። በሌሎች የአውሮፓ ከተሞችና ከአውሮፓ ውጭ ባሉ ሐገራት ከተሞችም ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል ።

ኢትዮጵያውያን በሐገር ውስጥም ሆነ ከሐገር ውጭ በከፍተኛ መጠን በአንድነት ቆመው የጋራ ድምፃቸውን ሲያስተባብሩ የቆዩ ቢሆንም ሚያዝያ 30 በአዲስ አበባ ጎዳናዎች የታየው ትዕይንት ፣ በክፍለ ሃገር ከተሞችም ተቃዋሚዎችን ለመደገፍ የወጣው ሕዝብ ብዛት ፣ እንዲሁም በዩኤስ አሜሪካ ዋሽንግተን ላይ የታየው ሰልፍ ከመቼውም ጊዜ በላይ የላቀ ፣ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የለውጥ ተስፋን የሰነቀ ሆኖ ቀጥሏል ። ይህ ትብብር ፣ መነሳሳትናበሕዝቡ ውስጥ በከፍተኝ ደረጃ የሰረፀው የለውጥ ስሜት ከእንግዲህ የጠመንጃ አገዛዝ በዚች ሐገር እንዲያበቃ የማድረግ ኃይል እንዳለውም ሊሰመርበት ይገባል ። በከፍተኛ ስሜት የተነሳሳንና ድሉን ማሽተት የጀመረ ሕዝብ ድምፁ ሲቀለበስ ፣ የጉልበት አገዛዝ ሲነግስ ከቶውንም በዝምታ አይመለከትም ። እንደተለመደው ነገሮችን በማምታታትና በማስፈራራት በመጣንበት መንገድ እንቀጥላለን የሚሉ ካሉ አቋማቸውን እንደገና ቢመረምሩ ከማንም በላይ ተጠቃሚዎች እነርሱ ይሆናሉ ።

ዛሬ ሥልጣን ላይ ያለው የአቶ መለስ መንግሥት የዛሬ 14 ዓመት ሥልጣን ላይ ሲወጣ የሶሻሊስቱ ጎራ ፈርሶ ፣ የካፒታሊዝም ርዕዮተዓለም ነግሶ ፣ ዓለም በተለይም ታዳጊ ሐገራት የልዕለ ኃያሏ ዩኤስ አሜሪካ ተከታይ ከመሆን ውጭ አማራጭ ያልነበረበት ሁኔታ ነበር ። በመሆኑም በትግል ላይ በነበረበት ወቅት እንደ ደርግ ሁሉ ሶሻሊዝምን ሲያቀነቅን የነበረውና እንዲያውም የአልባኒያ ሶሻሊዝም አድናቂና ተከታይ ሆኖ የዘለቀው የሕወሓት/ኢሕአዴግ ቡድን ወደ ስልጣን ሲመጣ ባሉት አስገዳጅ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎች የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትንና ሃሳብን የመግለጽ ነፃነትን በመቀበል በዚህች ሐገር የዴሞክራሲ መስረት እንዲጣል ማድረጉ በምንም የማይስተባበል ቢሆንም ፣ በሐገራችን ከነበሩት መንግሥታት ሁሉ ፍፁም በተለየ ሁኔታ በኢትዮጵያውያን ላይ ጥርጣሬንና ጥላቻን በማንገስ ፣ በኢትዮጵያውያን ኪሳራ ባዕዳንን ለማበልፀግ የተንቀሳቀሰ ፣ ዘረኝነትን ያነገሰ የጥላቻ ቡድን መሆኑን ፀሃይ በወጉ ያገኘው ሃቅ ነው ። ስለ ኢትዮጵያዊነት መናገር የተወገዘበት ፣ ስለ ባንዲራ ክቡርነት ማዜም እንደወንጀል የተቆጠረበት ፣ ሰዎች በእውቀታቸው ሳይሆን በዘራቸው ወደ ሥልጣን የተሰባሰቡበት ፣ በዘር ልዩነት ዕልቂት የነገሰበት ፣ ንፁሃን የተፈጁበትና የተጨፈጨፉበት አስቀያሚና አሳፋሪ ሁኔታን በኢትዮጵያ ያነገሰው ዛሬ በሥልጣን ላይ ያለው የአቶ መለስ ቡድን ነው ።


አቶ መለስ ስለ ኢትዮጵያውያን አንድነት የሚነገረውን ለማጣጣልና ልዩነትን ለማስፋት " የአክሱም ሃውልት ለወላይታው ምኑ ነው ?" ከማለታቸውም ባሻገር ታሪካዊውንና የነፃነት ተምሳሌት ሆኖ የዘለቀው ሰንደቅ አላማችን " ጨርቅ " ነው በማለት ማራከሳቸው የማይረሳ ነው ። ከግንቦት 1997 ምርጫ ዋዜማና ከምርጫው ወዲህ ስለ አክሱም ሃውልት የተናገሩትንና ስለ ባንዲራ የሰጡትን አስተያየት ማስተባበል ጀምረዋል ። ማስተባበያቸው ግን ፍፁም እውነትነት የለውም ። ዛሬ ከ 14 ዓመት በኃላ ጉዳዩን አንስቶ ምክንያት መደርደር ዋነኛ ግቡ በስልጣን ለመቀጠል ለኢትዮጵያውያን የተሰጠ የአፍ ጉቦ እንደሆነ ይታመናል ። አንዳንዶች እንደሚሉት ጠ/ሚ/ር መለስ ተፀፅተውም ከሆነ ከእሳቸው የሚጠበቀው የዕብሪት ንግግሮችን በውሸት መቀባባት ሳይሆን ፣ በይፋ ይቅርታ መጠየቅ ነው ። ከይቅርታም በላይ የሚሆነውና አቶ መለስ ዜናዊን ለዘለዓለም በመልካምነት የሚያስታውሳቸው ፣ የእስከዛሬውን ግፍና ጉድፍ ነቃቅሎ የሚጥልላቸው ግንቦት 7/1997 በሐገራችን የተከሄደውን የምርጫ ውጤት ያለአንዳች ማጭበርበር በፀጋ ሲቀበሉ ብቻ ነው ።

ታዛቢዎች ባሉባቸው አዲስ አበባን በመሳሰሉ ዋና ዋና ከተሞች በዜሮ የተሸኘው የአቶ መለስ ቡድን በገጠር በከፍተኛ ድምፅ አሸንፊያለው ሲል የሰጠው መግለጫ ጥርጣሬን የሚጋብዝ ከመሆኑም ባሻገር ፣ በተግባር ሲታይ በማጭበርበር የተሞላ ስለመሆኑም ማስረጃ ቀርቧል ። በመሆኑም የአቶ መለስ ቡድን ለሕዝብ ድምፅ በመገዛት በዚህች ሐገር ታሪክ መስራት ይጠበቅበታል ። ከእንግዲህ በጉልበት ለመቀጠል መሞከር የማያዋጣ እና ውርደትን የሚጋብዝ ከመሆኑም ባሻገር የስርዓቱን ወንጀልም የከፋ ያደርገዋል ። በጠመንጃ እንሞክረውና ካልሆነ እንሸሻለን የሚል ከልክ ያለፈ የስልጣን ጥም መድረሻው ከርቸሌ ሊሆን እንደሚችል ማሰቡ አይከፋም ።

ከስልጣን መውረድ የዓለም ፍፃሜ አይደለም ። በሰላማዊ መንገድ ስልጣን መልቀቅ እንደገና በሕዝብ ድምፅ ወደ ስልጣን ለመውጣት እና በፍቅር ለመኖር ዋስትና ነው ፤ አቶ መለስ ለሕዝብ ድምፅ ራሳቸውን አስገዝተው ለቀጣዩ ምርጫ ይዘጋጁ ። እርግጥ ነው ይህ በዘር የተቧደነና በጥቅም የተሳሳበ የእንብላው ማህበር ጥቅምና ስልጣን ከሌለ የሚበተን መሆኑ ቢታመንም ፣ ፍላጎቱ ካለ ጥቂት የተሻሉ ሰዎች ከብዙ ግብስብሶች የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆኑ የሚያጠራጥር አይሆንም ። ከዚህ ውጪ ይህቺን ሐገር በመበተን ለኤርትራ ነፃነትም ሆነ ለአሰብ ወደብ ዋስትና እናስገኛለን የሚለው ድብቅ አጀንዳ ተደርሶበታልና ከእንግዲህ አይሰራም ። "